
መንግስት 88 ኮንዶሚኒየሞች ጠፉብኝ ሲለን እግራችንን
ሰቅለን የሳቅን
፡
የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ጋምቤላ ላይ በጥይት ሲፈጁን
ከመንግስት ቀድመን ብሔራዊ የሀዘን ቀን ያወጅን
፡
ስለ እስራኤል መንግስት ሲወራ ክርስቲያን የተነካ
እየመሰለን ሙስሊም ወንድሞቻችንን የሰደብን
:
ስለ አረብ ሲወራ እስልምና የተነካ እየመሰለን ክርስቲያን
ወንድሞቻችንን ያስቀየምን
:
አባ ግርማ ከእስር እንዲፈቱ ዘመቻ የከፈትን
፡
የሙስሊም ኮሚቶዎች ነፃ እንዲዎጡ የታገልን
፡
ሶሪያ ውስጥ ህፃናት በቦንብ ሲጋዩ አይተን እንዳላየን ያለፍን
፡
ፈረንሳይ በሽብር ጥቃት ምክንያት በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች
ሲገደሉባት የፈረንሳይን ባንዲራ ለብሰን ስቅስቅ ብለን ያለቀስን
፡
ሳውዳረቢያ የመንን በጦር አውሮፕላን ስታፈራርስ ምናገባን
ብለን ጭጭ ያልን
፡
የማትሪክ ፈተና ተሰረቀ ሲባል የተገረምን…. ተገርመንም
ለሁሉም እንዲደርስ ሼር ያደረግን
፡
ህዝባችን በኤሊኖ ምክንያት በረሀብ ሲገረፍ የተመለከትን
:
ኢሀአዲግ መቶ ፐርሰንት አሸንፌያለው ብላ ድምፃችንን
ስትቀማን ድምፅ አልባ የሆንን
፡
እኛ ሰፈር ውሀ ለአንድ ሳምንት ስጠፋ ሮቤል ኪሮስ ግን ብራዚል
ድረስ ሄዶ ገላውን ሲታጠብ አይተን የታዘብን
፡
ሉሲ ከዛፍ ላይ ወድቃ ነው የሞተችው ሲሉን በሳቅ
የተንፈራፈርን
፡
የኦሮሚያን እና የአማራን አመፅ የደገፍን… በሞቱት
ወንድሞቻችን ክፉኛ ያዘንን
፡
በቻት የተዋወቅን…. የተጀናጀንን… የተጣበስን
፡
ሲሻን ኢትዮጲያዊ አንድነትን የሰበክን ሲሻን ደግሞ
በየኮሜንቱ በዘር፣ በሀይማኖት እና በጎሳ ተከፋፍለን የተሰዳደብን
፡
እኛ ማለት የገዛ ጠ/ሚኒስትራችን በገዛ ፍቃዱ መሳሪያ አስተኩሶ ያገሩን ልጅ ሲያስጨርስ ያየን
እኛ ማለት የታሰሩ ወንድሞቻችን በእሳት ሲቃጠሉ እኛ
ጨጓራችን የተጠበስን
እኛ ማለት…… ከ2008 እሳት ተርፈን ለ2009 ልንደርስ
የተዘጋጀን ፌስቡካውያን ነን፡፡